Search

የኢትዮጵያ ሕዝብ ስላከበረን አብዝተን ማክበር፣ ባከበረን ልክ ታምነን መገኘት አለብን፡- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

ቅዳሜ ሰኔ 13, 2018 54

የኢትዮጵያ ህዝብ በምርጫ ወቅት ያሳየው ታማኝነት እና ፍቅር የመንግሥት አገልግሎት እንዲሻሻል እና ሌብነት እንዲቀንስ ባለው ፍላጎት በመሆኑ፣ ይህን አደራ መጠበቅ ካልተቻለ  ቀጣይነት አደጋ ላይ እንደሚወድቅ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ለከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች አሳስበዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በንግግራቸው ወቅት አሁንም በየተቋማቱ በእጅ መንሻ እና በብልሹ አሰራር ምክንያት የሚማረሩ ዜጎች መኖራቸውን ተናግረው የኢትዮጵያ ህዝብ ስላከበረን አብዝተን ማክበር፣ ስላከበረን አብዝተን ማገልገል፣ ባከበረን ልክ ታምነን መገኘት አለብን  ሲሉ አስጠንቅቀዋል።

ቴክኖሎጂን ማስፋፋት ዋነኛ ጥቅሙ ሰብዓዊ ንክኪን በመቀነስ ሌብነትን ማስቀረት መሆኑን የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ የቢሮክራሲ መጉላላት ዜጎችን ለከፍተኛ ብስጭትና ለአደጋ እንደሚዳርግ አስገንዝበዋል።

በመሆኑም እያንዳንዱ ተቋም ራሱን ፈትሾ የቴክኖሎጂ አጠቃቀሙን በማሳደግ የህዝቡን የቅሬታ ምንጭ በአስቸኳይ ማድረቅ እንዳለበትና አሁን የተመዘገቡት ድሎች የህዝቡ ፍላጎት 1 በመቶ  ብቻ መሆናቸውን አስገንዝበዋል።