ዛሬ በ36ኛው ሳምንት የሊጉ መርሀ ግብር በአዲስ አበባ ስታዲየም 2ኛ ደረጃ ላይ የሚገኘውን ነጌሌ አርሲን የገጠመው ሲዳማ ቡና 1 ለ 1 አቻ ተለያይቷል።
የሲዳማ ቡናን ግብ ያስቆጠረው ብርሀኑ በቀለ ሲሆን፤ በረከት ወልዴ ነጌሌ አርሲን በፍፁም ቅጣት ምት አቻ አድርጓል።
በዚህም ነጥቡን 65 ያደረሰው ሲዳማ ቡና ሁለት ሳምንታት እየቀሩ ከወዲሁ የ2018 ሲቢኢ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ሻምፒዮን መሆኑን አረጋግጧል።