Search

ሲዳማ ቡና የ2018 ሲቢኢ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ሻምፒዮን ሆነ

ቅዳሜ ሰኔ 13, 2018 44

ዛሬ በ36ኛው ሳምንት የሊጉ መርሀ ግብር በአዲስ አበባ ስታዲየም 2ኛ ደረጃ ላይ የሚገኘውን ነጌሌ አርሲን የገጠመው ሲዳማ ቡና 1 ለ 1 አቻ ተለያይቷል።

የሲዳማ ቡናን ግብ ያስቆጠረው ብርሀኑ በቀለ ሲሆን፤ በረከት ወልዴ ነጌሌ አርሲን በፍፁም ቅጣት ምት አቻ አድርጓል።

በዚህም ነጥቡን 65 ያደረሰው ሲዳማ ቡና ሁለት ሳምንታት እየቀሩ ከወዲሁ የ2018 ሲቢኢ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ሻምፒዮን መሆኑን አረጋግጧል።