Search

7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ነፃ፣ ፍትሃዊና ዴሞክራሲያዊ በሆነ መንገድ የተካሄደ በመሆኑ የምርጫውን ውጤት አክብረን እንቀበላለን - የጋምቤላ ክልል ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት

ሰኞ ሰኔ 15, 2018 79

የህዝብን ድምፅ በማክበር 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ውጤት እንደሚቀበል የጋምቤላ ክልል የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ገለፀ

የምክር ቤቱ ሰብሳቢና በክልሉ የኢዜማ ምክትል መሪ ኮማንደር ጋትቤል ቦል ምርጫው ህዝቡ   ይበጀኛል ያለውን በነፃነት የመረጠበትና የፖለቲካ ፓርቲዎችም ዓላማና አማራጮቻቸውን በስፋት ለህዝብ ያቀረቡበት ሂደቶች ውስጥ ያለፈ በመሆኑ የህዝብን ውሳኔ በማክበር ውጤቱን በፀጋ እንቀበላለን ብለዋል።

በምርጫው ላይ ከፍተኛ ቁጥር ያለው ህዝብ በነቂስ ወጥቶ መሳተፉ በኢትዮጵያ የዴሞክራሲ ልምምድ እየዳበረ መምጣቱን የሚያሳይ ስለመሆኑም ተናግረዋል።

በአጠቃላይ የምርጫ ውጤት አሸናፊ ለሆነው ፓርቲና ለመራጩ ህዝብ እንኳን ደስ አላችሁ በማለት የደስታ መግለጫ መልዕክትም አስተላልፈዋል።

የህዝብ ድምፅ ትልቅ አደራ እና ሀላፊነት መሆኑን የጠቆሙት ኮማንደር ጋትቤል፡ የፖለቲካ ፓርቲዎች ልዩነቶችን በማጥበብ በአገራዊ ጉዳይ ላይ በመተባበር ከአሸናፊው ፓርቲ ጋር በመሆን የድርሻቸውን ሀላፊነት ሊወጡ እንደሚገባም ገልፀዋል።

በሚፍታህ አብዱልቃድር

አስተያየትዎን እዚህ ያስፍሩ: