የጨፌ ኦሮሚያ የ6ኛው የሥራ ዘመን፣ የ5ኛው ዓመት 11ኛ መደበኛ ጉባኤውን በጨፌ አዳራሽ ማካሄድ ጀምሯል።
በጉባኤው የ2018 በጀት ዓመት የሥራ አስፈጻሚ አካል የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት እና የ2019 ዓ.ም የዕቅድ አቅጣጫዎች፣ እንዲሁም የሕግ ተርጓሚ አካል የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት ለጨፌው አባላት ቀርቦ ውይይት ይደረግበታል።
የ2018 ዓ.ም ተጨማሪ በጀት 84 ቢሊዮን ብር፣ እንዲሁም የ2019 በጀት ዓመት 704 ቢሊዮን ብር የረቂቅ አዋጅ ለጨፌው ይቀርባል።
በተጨማሪም የዳኞች ሹመት ለጨፌው ቀርቦ ይጸድቃል ተብሎ ይጠበቃል።
በሃይማኖት ከበደ
አስተያየትዎን እዚህ ያስፍሩ: