የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሽመልስ አብዲሳ፣ የሰላም ጥሪውን ተቀብሎ በሰላማዊ መንገድ እታገላለሁ ለሚል አካል የተከፈተው የሰላም በር አይዘጋም ሲሉ ገለጹ።
የጨፌ ኦሮሚያ 6ኛው የሥራ ዘመን፣ የ5ኛው ዓመት 11ኛ መደበኛ ጉባኤ እየተካሄደ ይገኛል።
በዚህ ጉባኤ ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሽመልስ አብዲሳ የ2018 በጀት ዓመት የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት እና የ2019 ዓ.ም ዕቅድን እያቀረቡ ነው።
የክልሉ መንግሥት ከምንም በላይ ሰላምን ለማረጋገጥ እና የሕግ የበላይነትን ለማስከበር ከፍተኛ ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑን በሪፖርታቸው ገልጸዋል።
መንግሥት ሕዝቡን በሚገድል፣ በሚዘርፍ እና በሚያሸብር ኃይል ላይ ያልተቋረጠ የሕግ የበላይነትን የማስከበር እርምጃ እየወሰደ እንደሚገኝም ጠቁመዋል።
የክልሉ መንግሥት ከፌዴራል የፀጥታ ኃይሎች ቅንጅት እና ከሕዝቡ ትብብር ጋር በመሆን፣ በርካታ ቁጥር ያላቸውን የጥፋት ኃይሎች ማጥፋት፣ መማረክ እና እጃቸውን እንዲሰጡ ማድረግ መቻሉንም ተናግረዋል።
መንግሥት በአቋራጭ ሥልጣን ለመያዝ ካለው ሕልም ተስፋ መቁረጥ አቅቶት በጫካ ውስጥ የቀረውን ኃይል አድኖ ለሕግ እንደሚያቀርብ አቶ ሽመልስ ገልጸዋል።
አስተያየትዎን እዚህ ያስፍሩ: