የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን የሥራ ባልደረባ የነበሩት ወ/ሮ አልማዝ ነጋሽ ሥርዓተ ቀብራቸው በዛሬው ዕለት በወለቴ ለሚ ጽርሃ አርያም ቅድስት ሥላሴ ቤተክርስቲያን ተፈጽሟል።
ወ/ሮ አልማዝ ባደረባቸው ህመም በሕክምና ሲረዱ ቆይተው ነው በትናንትናው ዕለት በ60 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም በሞት የተለዩት።
ወ/ሮ አልማዝ በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን የኦሮምኛ ፕሮግራም ክፍል የክፍሉን የዜና ቅንብር የፕሮግራም ሥራ እና በኦሮምኛ የዜና እወጃ ክፍለ ጊዜ የሚተላለፉ የጽሁፍ ሥራዎችን በመሥራት በቅንነት፣ በታማኝነትና በታታሪነት አገልግለዋል።
ከ1986 ዓ.ም እስከ 2015 ዓ.ም ለ29 ዓመታት ኢቢሲን ያገለገሉት ወ/ሮ አልማዝ ነጋሽ፣ በአገልግሎት ዘመናቸው ለተቋሙ የሚጠበቅባቸውን አገልግሎት ሲያበረክቱ ቆይተዋል።
ወ/ሮ አልማዝ ባለትዳር እና የአንድ ሴትና የአንድ ወንድ ልጆች እናት ነበሩ።
የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ለሥራ ባልደረቦች እና ለወዳጅ ዘመዶች መጽናናትን ይመኛል።
አስተያየትዎን እዚህ ያስፍሩ: