በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፕሬዚዳንት አቶ አቤ ሳኖ የተመራው የባንኩ ከፍተኛ የሥራ አመራር ቡድን በመሐል አዲስ አበባ እየተገነባ ያለውን ‘አራዳ ሌግዠሪ ሞል’ የአፈጻጸም ሂደት በቦታው ተገኝቶ ጎብኝቷል።
ከታሪካዊው የዓድዋ ድል መታሰቢያ፣ ከአራዳ ፓርክ እና ከወንዝ ዳርቻ ልማት ጋር በተናበበ መልኩ የሚገነባው ዘመናዊ ሞል ለመዲናዋ ውበት የሚጨምር፣ ኢኮኖሚውን የሚያነቃቃ እና ለበርካቶች የሥራ ዕድል የሚፈጥር የንግድ ማዕከል ስለመሆኑ ተገልጿል።
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፕሬዚዳንት አቶ አቤ ሳኖ በጉብኝቱ ወቅት፣ ባንኩ ለዚህ ፕሮጀክት የሚያደርገውን ድጋፍ አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸው፤ ህንጻው በተያዘለት የጊዜ ሰሌዳ በጥራት እንዲገነባ በቁርጠኝነት እንደሚሠራ ማረጋገጣቸውን የባንኩ መረጃ ያመለክታል።
115 ሺህ ካሬ ሜትር አጠቃላይ የህንፃ ስፋት ያለው “አራዳ ሌግዠሪ ሞል” ሱፐር ማርኬቶች፣ ሲኒማ፣ ጂምናዚየም፣ ባንኮች፣ የውጭ ምንዛሬ ማዕከላት፣ ክሊኒኮች፣ ሬስቶራንቶች፣ ካፌዎች እና ሌሎች አገልግሎቶችን ያካተተ ሁለገብ የንግድ፣ የአገልግሎትና የመዝናኛ ማዕከል ሆኖ እንደሚገነባ ተገልጿል።
አስተያየትዎን እዚህ ያስፍሩ: