Search

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ካቢኔ 6ኛ ዓመት 1ኛ መደበኛ ስብሰባ በዛሬው ዕለት አካሄደ

ዓርብ ነሐሴ 15, 2018 152

 

ካቢኔው በዛሬው ስብሰባው በቀረቡ  አጀንዳዎች ላይ ተወያይቶ  ውሳኔዎችን  አስተላልፏል፡፡

በዚህ መሠረት፦                    

1- የማህበረሰብ ጤና አቀፍ መድህን ተጠቃሚዎች መዋጮን ለማሻሻል የቀረበ የውሳኔ ሀሳብ ተወያይቶ ተግባራዊ እንዲሆን አፅድቋል።

2- ሀገራዊ ፋይዳ ላላቸው ፕሮጀክቶች (ለሆቴል፣ ለሞልና አፓርትመንት፣ ኢንዱስትሪ፣ ለበጎ አድራጎት፣ መንግስታዊ ተቋማት እና የህክምና ተቋማት) የማስፋፍያና አዳዲስ የመሬት ጥያቄዎችን ለመመለስ የቀረበ የውሳኔ ሀሳብ ላይ ተወያይቶ ተፈፃሚ እንዲሆን አፅድቋል።

3- በከፊል በኮሪደር ለምተው፣ በከፊል ሳይለሙ የቆዩ አካባቦዎችን በተሟላ ሁኔታ ለማልማት የቀረበ የውሳኔ ሀሳብ ላይ ተወያይቶ ተግባራዊ እንዲሆን አፅድቋል።

 

 

 

አስተያየትዎን እዚህ ያስፍሩ: