ዛሬ በኅብር ቀን አሮጌውን ዓመት አልፈን ወደ አዲስ ዓመት መሸጋገርን ከሚያበስሩ ውብ እና ህብራዊ ባህሎቻችን መካከል የሆኑትን የአበባአየሽ ወይ፣ የአሸንዳ፣ ጎቤ፣ ሽኖዬ፣ ሻደይ ጭፈራዎች በከተማችን በታሪካዊው የአድዋ ድል መታሰቢያ በድምቀት ተከብረዋል።
ኢትዮጵያ የበለፀገ የህብረተሰብ ሀብት ክምችት ያላት ሀገር ናት። የመደመር መንግሥትም እነዚህን ሀብቶች በመጠበቅ፣ በመንከባከብና በማልማት ለሀገር እድገትና ለህብረተሰብ ልማት ማዋል ላይ ልዩ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ነው።
ህብረብሔራዊት በሆነችው ከተማችንም ውብ ኢትዮጵያዊ ባህሎቻችን ጎልተው እንዲወጡ፣ ከባህሉና እሴቱ ማግኘት የሚገባንን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ጥቅም እንዲያስገኙ እና የቱሪዝም መስህብ እንዲሆኑ እየሰራን እንገኛለን።
አስተያየትዎን እዚህ ያስፍሩ: