Search

ቻይና 165 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሜትር አዲስ የጋዝ ክምችት አገኘች

ቅዳሜ ነሐሴ 17, 2017 52

የተፈጥሮ ጋዙ የተገኘው በመካከለኛው ቻይና ሁቤ ግዛት ውስጥ መሆኑን ቻይና አስታውቃለች፡፡

በአካባቢው የተገኘው አዲስ የጋዝ ክምችት በቀን እስከ 323 ሺህ ኪዩቢክ ሜትር ጋዝ ማውጣት የሚያስችል ነው ተብሏል፡፡

የተፈጥሮ ጋዙ የተገኘበት ቦታ የነበረው መልከካ ምድራዊ አቀማመጥ እና የተነሳ የፍለቃ ሥራውን ውስብስብ አድርጎት የነበረ ቢሆንም በኋላ ላይ ግን የተገኘው ውጤት እጅግ አመርቂ እንደሆነ የፕሮጀክቱ  ኃላፊዎች ተናግረዋል፡፡

በተለምዶ የሼል ጋዝ ተብሎ የሚጠራው የጋዝ አይነት ከሚቴን የጋዝ አይነቶች የሚመደብ ሲሆን በአብዛኛው ጊዜ በአለታማ ስፍራዎች ውስጥ የሚገኝ እና በብዙ ቦታዎች የማይገኝ ነው፡፡

በርካታ ጥቅሞች ያሉት ይህ ጋዝ ለኢንዱስትሪዮች ኃይል ለማቅረብ ይረዳል። በዚህም ኢንዱስትሪዎች ዝቅተኛ የካርበን ልቀት እንዲኖራቸው ያግዛል ሲል ሲጂቲኤን ዘግቧል።

 

በሃብተሚካኤል ክፍሉ