Search

ፕሬዚዳንት ፑቲን ሩሲያ ከዩክሬን ጋር ድርድር እንደምታደርግ አሳወቁ

እሑድ ነሐሴ 18, 2017 62

የሩሲያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሰርጌ ላቭሮቭ እንዳስታወቁት ፕሬዚዳንት ፑቲን ከአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ጋር በስልክ ባደረጉት ውይይት ሩሲያ በቱርኪዬ ኢስታንቡል የጀመረችውን ቀጥተኛ ድርድር ከዩክሬን ጋር ለመቀጠል ዝግጁ መሆኗን ገልጸዋል።
ላቭሮቭ አክለውም የሩሲያ እና የዩክሬን ልዑካን በኢስታንቡል ፊት ለፊት ተገናኝተው እንደሚወያዩም መግለጻቸውን ሲጂቲኤን ዘግቧል።
ሩሲያ እና ዩክሬን በቱርኪዬ ኢስታንቡል ከአንድ ወር በፊት የሰላም ድርድር አድርገው ነበር። ድርድሩ ያለበቂ ስምምነት መጠናቀቁ ይታወሳል።
ይሁንና የአሁኑ ውይይታቸው መቼ እንደሚደረግ ዘገባው በግልጽ ያለው ነገር የለም።