Search

ሕንድ ውቅያኖስን ከአፍሪካ ጋር የሚያገናኝ የኢኮኖሚ ዞን

ሰኞ ነሐሴ 19, 2017 43

የጃፓኑ ጠቅላይ ሚንስትር ሺጌሩ ኢሺባ ሀገራቸው ሕንድ ውቅያኖስን  ከአፍሪካ ጋር የሚያገኝ አዲስ የኢኮኖሚ ዞን ለመመስረት እንደምትፈልግ ሀሳብ አቅርበዋል።

ጠቅላይ ሚንስትሩ በጃፓን በተካሄደው ዓለም አቀፉ የአፍሪካ ልማት ኮንፈረንስ ላይ ሀገራቸው የሕንድ ውቅያኖስ አካባቢ ከአፍሪካ አህጉር  ጋር በማገናኘት የንግድና ኢንቨስትመንት ትብብሯን ለማሳደግ እንደምትሠራ ተናግረዋል።

ጃፓን ከ30 ሺህ በላይ አፍሪካውያን ባለሙያዎችን በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ በማሰልጠን ዲጂታል አሠራርን ለመፍጠር እና የአፍሪካ ልማት ባንክን ለመደገፍ ዝግጅቷን ማጠናቀቋን ገልጻለች።

በሀብተሚካኤል ክፍሉ

#Japan #Africa #Indianocean