Search

ሰባቱን የጉባ ብስራቶች በአጭር ጊዜ በመፈፀም ሶስተኛው ዓድዋችንን እንደግማለን - ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ

ሓሙስ መስከረም 08, 2018 28

ሰባቱን የጉባ ብስራቶች በአጭር ጊዜ በመፈፀም ሶስተኛው ዓድዋችንን እንደግማለን ሲሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ ተናገሩ።

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ በስኬት መጠናቀቁን በማስመልከት ታላቅ ሕዝባዊ ሰልፍ በወላይታ ሶዶ ከተማ ተካሂዷል።

በመርሐ ግብሩ ላይ የተገኙት ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ ዳግማዊ ዓድዋ የሆነውን ሕዳሴ እውን ለማድረግ፤ ኢትዮጵያውያን የከፈሉት ዋጋ ታላቅ መሆኑን ገልጸዋል።  

ጥቃቅን ልዩነቶችን ወደ ጎን ትተን በአንድ ልብ ከሠራን 3ኛው ዓድዋችን በቅርቡ እውን ይሆናል ብለዋል ርዕሰ መስተዳድሩ 

በዓድዋ ጊዜ በአንድነት ታሪክ ሰርተናል ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ፣ 2ኛው ዓድዋችን ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብበፈተናዎች መካከል በተባበረ ክንድ እውን መሆኑን ተናግረዋል። 

አሁን ጊዜው 3 ዓድዋ የምንዘጋጅበት ነው ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ፥ በዓድዋ ጊዜ እንደነበረው ሁሉ አንድ ከሆንን ሀገር በመለወጥ ሌላ ታሪክ በአጭር ጊዜ መስራት እንችላለን ብለዋል። 

ይህንን ለማሳካት በአንድነት ተግቶ መስራት ያስፈልጋል ሲሉም ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል።

በተመስገን ተስፋዬ