Search

የመደመር መንግሥት መጽሐፍ ሀገርን ማሻገሪያ መንገዶችን ቁልጭ አድርጎ አሳይቷል - ፍፁም አሰፋ (ዶ/ር)

ሓሙስ መስከረም 08, 2018 31

የፕላንና ልማት ሚኒስትር ፍፁም አሰፋ (/) የመደመር መንግሥት መጽሐፍ ሀገርን ማሻገሪያ መንገዶችን ቁልጭ አድርጎ ያሳየ መሆኑን ገልጸዋል።

መጽሐፉ ሶስት ጊዜ መብላት ከሚለው በእጅጉላቀ ምናባዊ ከፍታ ተጨባጭ የሆኑ ሕልሞችን እና ሀገርን ማሻገሪያ መንገዶችን ቁልጭ አድርጎ አሳይቷል ብለዋል።

የመንግሥታዊ እናማህበራዊ አገልግሎቶች ማሻሻያ ላይ የመፍትሔ ሀሳቦችን የያዘ መጽሐፍ መሆኑንም /ር ፍፁም ተናግረዋል።

መጽሐፉ ፍጥነት፣ ፈጠራ እና ዝላይ በማለት ያመላከታቸውን ሀገር ማሻገሪያ መንገዶች በዝርዝር እንደሚያብራራ አንስተዋል።

የሀገሪቱ ዲጂታል ሽግግር ጉዞ የቴክኖሎጂ መሠረት ልማትን ከማጠናከር እና አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችን ከመዘርጋት መጀመርንዳለበትመጽሐፉ በግልጽ መቀመጡን ጠቅሰዋል።

ተቋማትአሠራር ሥርዓቶቻቸውን በቴክኖሎጂ በማዘመን አገልግሎቶችን በኦንላይን እንዲሰጡ እና እርስ በርስ እንዲቀናጁ ማድረግ ወሳኝ መሆኑን ተናግረዋል።

የመደመር መንግሥት እሳቤ ባለፉት ጥቂት ዓመታት ከከተማ እስከ ገጠር በተለያዩ መስኮች ተተግብሮ በርካታ ተጨባጭ ለውጦች ማምጣቱንም ነው ሚኒስትሯ የገለጹት።

በቢታንያ ሲሳይ

#EBCdotstream #Ethiopia #YemedemerMengist