Search

በኢትዮጵያ በዓይነቱ የመጀመሪያ የሆነ የወባ መከላከያ ክትባት

ሓሙስ መስከረም 08, 2018 33

የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ደረጀ ዱጉማ በኢትዮጵያ የመጀመሪያ የሆነውን የወባ መከላከያ ክትባት በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል፣ ደቡብ ኦሞ ዞን፣ ቱርሚ ከተማ ዛሬ አስጀምረዋል።

ክትባቱ ውጤታማነቱ በዓለምጤና ድርጅት የተረጋገጠና አስተማማኝ መሆኑን ዶ/ር ደረጀ ዘመቻውን ባስጀመሩበት ወቅት ተናግረዋል።

ዕድሜያቸው ከ5 ዓመት በታች ለሆነ ህፃናት በዘመቻ መልክ የሚሰጠው ክትባት የወባ ስርጭት ያለባቸው 58 ወረዳዎችን እንደሚያካልል ገልጸዋል።

በእነዚህ አካባቢዎት የሚኖሩ ወላጆችና አሳዳጊዎች ህፃናቱን በማስከተብ ግዴታቸውን እንዲወጡ ጥሪ ቀርቧል።

ከክትባቱ በተጨማሪ 3.5 ሚሊዮን በላይ የአልጋ አጎበሮችወባ ተጋላጭ ለሆኑ አካባቢዎች እንደሚሰራጩ ተገልጿል።

በተመስገን ተስፋዬ

#EBCdotstream #Ethiopia #Malaria #Vaccination