Search

ከራሱ ጥረት በተጨማሪ በመምህሮቹና በወላጆቹ የቅርብ ድጋፍ ለውጤት መብቃቱን የሚናገረው ተማሪ ሐምዛ

ሓሙስ መስከረም 08, 2018 52

በትጋት ትምህርቴን በመከታተሌ እና በማጥናቴ ከፍተኛ ውጤት ለማምጣት ችያለሁ ሲል 12 ክፍል መልቀቂያ ሀገር አቀፍ 549 ያመጣው በሶማሊ ክልል፣ ጅግጅጋ ከተማ ስፓርክአካዳሚ ተማሪው ሐምዛ ሻም መሐመድ ገለጸ።

ተጓዳኝ መጻሕፍትን በማንበብ፣ ያለፉ 12 ክፍል መልቀቂያ ሀገር አቀፍ ፈተናዎችን በመሥራት፤ ከባባድ ጥያቄዎች ሲያጋጥሙትም ከትምህርት ሰዓት ወጪ መምህራንን ጠይቆ በመረዳት ለፈተናው በቂ ዝግጅት ማድረጉን ተማሪ ሐምዛ ይናገራል።

የራሱ ያላሰለሰ ጥረት፣ የትምህርት ቤቱ አስተዳደር እና የመምህሮቹ ያልተቋረጠ እገዛ እንዲሁም የወላጆቹ የቅርብ ክትትል እና ድጋፍ ለውጤታማነቱ ትልቅ አስተዋፅዖ ማድረጉን በመግለጽ ምስጋና አቅርቧል።

የሕክምና ሙያ ተምሮ በጤና አገልግሎት ዘርፍ በመሰማራት ሀገሩን እና ህዝቡን ማገልገል የሐምዛወደፊት ዕቅዱ ነው።

አባቱ አቶ ሻም መሐመድ በበኩላቸው ልጃቸው ሐምዛ በአልባሌ ነገሮች ሳይዘናጋ ጠንክሮ በመሥራቱ ለውጤት መብቃቱን ገልጸው፤ በሂደቱ እርሳቸውም ለዝግጅቱ የሚያስፈልጉ ግብዓቶችን ከማሟላት ጀምሮ ሁኔታዎችን በማመቻቸት እገዛ ማድረጋቸውን ተናግረዋል።

በቢታንያ ሲሳይ

#Ethiopia #Education #12thgrade #Exam #highscore