Search

የወላይታ ብሔር የባህል፣ የታሪክና የቋንቋ ሲምፖዚየም ተካሄደ

ቅዳሜ መስከረም 10, 2018 170

ዛሬ በወላይታ ሶዶ የተካሄደው ሲምፖዚየም ብሔሩ ያሉትን ባህል፣ የቋንቋና ሌሎች እሴቶች ለማሳደግ ትልቅ ድርሻ እንዳለው ተገልጿል።

የወላይታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ሳሙኤል ተሰማ፥ የብሔሩ ቋንቋና ባህሉ ሳይበረዝ ለቀጣዩ ትውልድ እንዲተላለፍ ለማድረግ በርካታራዎች እየተከናወኑ ነው ብለዋል።

በዚህም ከጊዜ ወደ ጊዜ ቋንቋውን ለማወቅና ባህሉንም ለመጠበቅ  የሚጥር ትውልድ እየተፈጠረ እንደሆነ አንስተዋል።

የወላይታ ዞን ባህልና ቱሪዝም መምሪያ ሀላፊ ምህረቱ ሳሙኤል በበኩላቸው፥ በተደረጉ ጥረቶች በዞኑ ተማሪዎች በአፍ መፍቻ ቋንቋቸው እንዲማሩ እንዲማሩ እና የዞኑ የሥራ ቋንቋ ወላይትኛ እንዲሆን ማድረግ መቻሉን አንስተዋል።

የወላይታ ብሄር የዘመን መለወጫ "ጊፋታ" በዓል በነገውለት በድምቀት ይከበራል።

በአታላይ ፀሐይ

#EBCdotstream #Ethiopia #Wolaita #NewYear #Gifata