Search

የሺህ ዘመናት አብሮነት እና የእርስ በርስ ትሥሥር አንፀባራቂዎቹ በዓላት

እሑድ መስከረም 11, 2018 49

የባህል እና ስፖርት ሚኒስትሯ ሸዊት ሻንካ ለወላይታ፣ ለጎፋ እና ጋሞ ዞን ሕዝቦች ዘመን መለወጫ በዓላት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።

ሚኒስትሯ በእንኳን አደረሳችሁ መልዕክታቸው እንደገለጹት፣ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የበርካታ ውብ ባህሎች፣ እሴቶች፣ ታሪኮች እና የብዝኃ ማንነቶች ባለቤት የሆነ ክልል ነው።

ከዚህ ውስጥ የወላይታ፣ የጋሞ እና የጎፋ ዞን ሕዝቦች የዘመን መለወጫ በዓላት ተጠቃሽ መሆናቸውን ጠቁመዋል።

በዓላቱ እንደየብሔረሰቡ ትውፊት እና ባህላዊ ዕሴት፡- በወላይታዮዮ ጊፋታ' በጋሞ ማስቃላ' በጎፋዎች ዘንድጋዜ ማስቃላ' በኦይዳ ብሔረሰብዮኦ ማስቃላ' በሚል ስያሜ እንደሚከበሩም ገልጸዋል።

እንዲሁም በዛይሴቡዶ ኬሶ' እና በጊዲቾባላ ካዳቤ' በሚል በተቀራረበ ወቅት ከዘመን ዘመን ላሸጋገረ ፈጣሪ ምስጋና በማቅረብ፣ በአብሮነት እና በአንድነት የሚከበሩ ድንቅ እሴቶቻችን ናቸው ብለዋል።

የበዓላቱ አከባበር የሕዝቡን የሺህ ዘመናት አብሮነትን፣ የእርስ በርስ መስተጋብር እና ትሥሥር ከማንፀባረቃቸውም በላይ ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ እንዳላቸው ሚኒስትር ሸዊት ገልጸዋል።

ስለሆነም ይህንን ውብ ባህል በመጠበቅ እና በማልማት የበለጠ ማጠናከር ይገባል ብለዋል።

በዓሉ የሰላም፣ የአብሮነት እና የአንድነት እንዲሆን መልካም ምኞታቸውን ገልጸዋል።

#Ethiopia #YooYooGifaataa #YooMaskala #YoGazeMaskala #YooOMaskala #YooYooBalaKadabe #YooYooBudoKeso