Search

የሕዳሴ ግድብ የኢትዮጵያ ልጆችን ለልማት ያስተባበረ፣ የመደመር ዕሳቤ የታተመበት ፕሮጀክት ነው፡- የምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ

ሰኞ መስከረም 12, 2018 32

የሕዳሴ ግድብ ከጫፍ እስከ ጫፍ በሁሉም የኢትዮጵያ ማዕዘናት የኢትዮጵያ ልጆችን ለልማት ያስተባበረ፣ የመደመር ዕሳቤ የታተመበት ፕሮጀክት ነው ሲሉ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ።
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት፤ ከተለያዩ የኢትዮጵያ ተራሮች በሸለቆ እና በሜዳ ገሰግሶ እንደሚገናኘው፣ ታላቁ ዓባይ የብዝኅነት ቤት በሆነችው ድሬዳዋ የሕዳሴ ግድብ መጠናቀቅን ተከትሎ ዛሬ የድጋፍ ሰልፍ ተደርጓል ብለዋል፡፡
በሕዳሴ ግድብ ያየናቸው በፈተናዎች መካከል እንደ አለት ጸንቶ በመቆም ማሸነፍ በደሬዳዋ ያሉ የልማት አቅሞችን ለሀገር ልማት ለማዋል ብርታት ይፈጥራል ብለዋል፡፡
ድሬዳዋ የሰላም እና የፍቅር ብቻ ሳይሆን ልማት እና ለለውጥ መበርታትም መገለጫዋ ነው ሲሉም ገልጸዋል ።

አስተያየትዎን እዚህ ያስፍሩ

ተያያዥ ዜናዎች: