Search

የሪሜዲያል ፕሮግራም ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገቡ ተማሪዎችን ቁጥር ለማሳደግ አስተዋጽኦ እያደረገ ነው

ረቡዕ መስከረም 14, 2018 59

ላለፉት ዓመታት ሲተገበር የነበረው የሪሜዲያል (አቅም ማሻሻያ) ፕሮግራም 12 ክፍል አገር አቀፍ ፈተና ወስደው ማለፊያ ነጥብ ማምጣት ያልቻሉ ተማሪዎች ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገቡበትንድል ማመቻቸቱን ትምህርት ሚኒስቴር ገለጸ።

የሪሜዲያል ፕሮግራሙ መንግሥት ለትምህርት ጥራት ያለውን ቁርጠኝነት ያሳየበትም ነው ሲሉ በሚኒስቴሩ የአስተዳደር እና መሠረተ ልማት መሪ አስፈፃሚ ሰለሞን አብርሃም (/) ከኤፍ ኤም አዲስ 97.1 ጋር በነበራቸው ቆይታ ገልጸዋል።

12 ክፍል ማጠቃለያ አገር አቀፍ ፈተና ወስደው ማለፊያ ነጥብ ማምጣት ያልቻሉ ተማሪዎች ለአንድ ተጨማሪ ዓመት በሚሰለጥኑበት በዚህ ፕሮግራም በአገር አቀፍ ፈተናው ካለፉ ተማሪዎች 3 እጥፍ የሚሆኑ ተጨማሪ ተማሪዎች ወደ ዩኒቨርሲቲዎች እንዲገቡ የማብቃት ሥራ ይከናወናል ብለዋል።

የሪሜዲያል ፕሮግራሙ ተጠቃሚዎች በሁሉም አማራጮች (በግል እና በመንግሥት ተቋማት) ፕሮግራሙን ከተከታተሉ በኋላ የሚፈተኑትን ፈተና 50 በመቶ በላይ ማምጣት ይጠበቅባቸዋል ነው ያሉት።

የሪሜዲያል ፕሮግራሙ ከፍተኛ በጀት ተመድቦለት በዩኒቨርሲቲ መምህራን እንደሚሰጥ ጠቅሰው፤ በቀጣይም ወደ ፕሮግራሙ ለሚገቡ ተማሪዎች ስልጠና የመስጠት ሥራው የዩኒቨርሲቲዎችን የመቀበል አቅም ባማከለ መልኩ ተጠናክሮ አንደሚቀጥል ተናግረዋል።

ጥራት ያለው ትምህርት ተደራሽማድረግ ብቁ፣ በራሱ የሚተማመን እና በየትኛውምዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ የሆነ የተማረ የሰው ኃይል ለማፍራት መንግሥት በቀረፀው ፖሊሲ መሠረት በርካታራዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ ብለዋል።

በንፍታሌም እንግዳወርቅ

#EBCdotstream #MoE #RemedialProgram