Search

በጋምቤላ ከተማ የኢሬቻ በዓል እየተከበረ ነው

ቅዳሜ ጥቅምት 08, 2018 59

በጋምቤላ ክልል የኢሬቻ በዓል በመልካ ባሮ በድምቀት በመከበር ላይ ይገኛል፡፡

በክልሉ በጋምቤላ ከተማ ኢሬቻ "መልካ ባሮ" ሲከበር የዘንድሮው ለ5ኛ ጊዜ ነው፡፡

ኢሬቻ በኦሮሞ ህዝብ ዘንድ ትልቅ ስፍራ የሚሰጠውና ፈጣሪን ለማመስገን በየዓመቱ የሚከበር ታላቅ በዓል ነው፡፡

በጋምቤላ ከተማ እየተከበረ በሚገኘው የኢሬቻ በዓል አባ ገዳዎች፣ ሀደ ሲንቄዎች እንዲሁም ቄሮና ቀሬዎችን ጨምሮ የተለያዩ የማህበረሰብ ክፍሎች ተሳትፈዋል፡፡