Search

ኢትዮጵያ በተከተለችው አዲስ የከተማ አተያይ ፖሊሲ፣ ተጨባጭ ኢኮኖሚያዊ እና ማኅበራዊ ለውጦችን ማስመዝገብ ችላለች

ቅዳሜ ጥቅምት 08, 2018 47

በኢትዮጵያ አሁን አሁን አዳዲስ ከተሞች እየተመሠረቱ፣ ነባሮቹም በቆዳ ስፋት እና በነዋሪዎች ብዛት እያደጉ መሆኑ በግልጽ ይታያል።

በሀገሪቱ የከተሞች ዓመታዊ የዕድገት ምጣኔ በአማካኝ 5.4 በመቶ እንደሆነ መረጃዎች ይጠቁማሉ።

የከተሞች ዕድገት እና መስፋፋት ከኢኮኖሚድገት ጋር የተያያዝ ሲሆን፤ ለአብነትም ቻይና፣ ብራዚል እና አርጀንቲና በዚህ ረገድ በፍጥነት ካደጉ ሀገራት መካከል ይጠቀሳሉ።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (/) በመደመር መንግሥት መጽሐፋቸው፥ ከተሞች በባህሪያቸው የሀገራት የሳይንስ፣ኢኖቬሽን የኃይልድገት ማሳለጫ መሆናቸውን ያነሳሉ።

የከተማ መሠረተ ልማት ሚኒስትሯ የፖሊሲ አማካሪ ያሬድ ተሾመ (/) ከኤፍ ኤም አዲስ 97.1 ጋር ነበራቸው ቆይታ፥ ከተሞች የኢኮኖሚድገት ማሳለጫ ይሆኑ ዘንድ 5 ዘርፎች ላይ በትኩረት መሥራት እንደሚገባ የመደመር መንግሥት መጽሐፍን ዋቤ አድርገው ተናግረዋል።

እነርሱም ኢንዱስትሪያላይዜሽን፣ ኢኖቬሽን፣ ንግድ፣ ሥራ ፈጠራ እና ዲጂታላይዜሽን መሆናቸውን ጠቅሰው፤ እነዚህን ማዕከል ያደረገ ከተማ መፍጠር እንደሚገባ ገልጸዋል።

ኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት ነባር ከተሞችንማደስ እና አዳዲስ ከተሞችንመፍጠር አዲስ የከተማ አተያይ ፖሊሲ እየተከተለች መሆኑን አንስተው፤ በዚህም ተጨማጭ ኢኮኖሚያዊ  እና ማኅበራዊ ለውጦችን ማስመዝገብ መቻሏን አክለዋል።

የአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት የኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ተስፋዬ ዘውዱ በበኩላቸው፥ ዲጂታል ኢትዮጵያ እውን በማድረግ ከተሞችንማስተሳሰር እና የአገልግሎት አሰጣጥን ቀልጣፋ ለማድረግ ስማርት ሲቲን መገንባት ዋነኛ አቅጣጫ ስለመሆኑ አብራርተዋል።

ይህንኑ የስማርት ሲቲ ፖሊሲ አሁን ላይ ከመዲናዋ አዲስ አበባ አልፎ ክልሎችም ላይ ተግባራዊ ለማድረግ ሥራ ስለመጀመሩም ነው ያነሱት

በሜሮን ንብረት

#etv #ebcdotstream #ethiopia #YemedemerMengist #cities #smartcities