Search

በጎ አድራጎትን ከውጭ ዜግነት እና እርዳታ ጋር የማያያዝ ትርክትን መቀልበስ ችለናል - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

ማክሰኞ ጥቅምት 11, 2018 47

በተከናወኑ ሰው ተኮር ሥራዎች በጎ አድራጎትን ከውጭ ዜግነት እና እርዳታ ጋር የማያያዝ ትርክትን መቀልበስ ችለናል ሲሉ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ።

“መስጠት አያጎድልም፣ በጎ ፈቃደኝነት ለሀገር ማንሰራራት” በሚል ለ2017 ዓ.ም በጎ ፈቃደኞች የእውቅና እና የሽልማት መርሐ-ግብር ተካሂዷል።

ባለፉት 7 ዓመታት 42.5 ቢሊዮን ብር የሚገመቱ የበጎ አድራጎት ሥራዎች የተከናወነ ሲሆን፤ ከ40 ሺህ በላይ የአቅመ ደካሞች ቤቶችን ማደስ ተችሏል ሲሉ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገልጸዋል።

በተጠቀሰው ወቅት በተደጋጋሚ በተከናወነ የማዕድ ማጋራት ሥራም ከማዕድ ባሻገር ፍቅርን ማጋራት እንደተቻለም ከንቲባ አዳነች አክለዋል።

በ2017 ዓ.ም ብቻ 16.1 ቢሊዮን ብር የሚገመቱ የተለያዩ የበጎ አድራጎት ሥራዎች መከናወናቸውን ገልጸው፤ ግለሰቦች፣ ባለሀብቶች፣ ተቋማት፣ ሲቪክ ማኅበራትን ጨምሮ ይህ እንዲቻል ላደረጉ በጎ አድራጊዎች ምስጋና አቅርበዋል።

አዲስ አበባ ከበጋ እስከ ክረምት እየሰጠችው ባለው የበጎ አድራጎት አገልግሎት በሀገሪቱ ካሉ ክልሎች ባለፈ በአፍሪካ ላሉ 15 ሀገራት ምርጥ ተሞክሮዋን እያካፈለች ስለመሆኑም ተገልጿል።

በሰናይት ብርሃኔ

#ebcdotstream #addisababa #communityservice #socialresponsibility