Search

ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ በ5ኛ ዓመት ዝክረ ሰሜን ዕዝ መርሐ-ግብር ላይ ባደረጉት ንግግር ያነሧቸው ዋና ዋና ነጥቦች

ሰኞ ጥቅምት 24, 2018 61

መከላከያ ሠራዊት ሕይወቱን ከሰጠለት ሕዝብ ውስጥ የወጡ ጥቂት ካሃዲዎች ጥቅምት 24 ቀን 2013 . ከኋላው መውጋታቸው ሕመሙ ጥልቅ ነው

በሰሜን ዕዝ ላይ የተፈፀመው ክህደት ወንድም ወንዱሙ ላይ የፈፀመው ክህደት በመሆኑ በታሪክ ልዩ ያደርገዋል

የመከላከያ ሠራዊት የአሸናፊነት ምሥጢር የአባቶቹን አርበኝነት መውረሱ ነው

የኢትዮጵያ ገዢ ባሕሪው የአርበኝነት ቢሆንም ሀገሪቱ ባንዳም ነበራት፣ አላትም 

የትግራይ ሕዝብ በሰሜን ዕዝ ላይ የተፈጸመውን ክህደት አይቀበለውም

የትግራይ ሕዝብ በልጆቹ ክህደት አፍሮ፣ ተመልሰን መቐለ ስንገባ አጨብጭቦ ተቀብሎን ነበር

ስለዚህ ክህደት እና አስናዋሪ ታሪክ ስናውራ ስለ ጥቂት የሕወሓት አመራሮች እንጂ ስለ ትግራይ ሕዝብ አይደለም

ይህ ጉጅለ በሻዕቢያ ተቀጥሮ ሀገር ያስገነጠለ እና የባህር በር ያሳጣን ነው

የትግራይ ወንጀለኛው ጉጅለ የትግራይን ሕዝብ ዕጣ ፈንታ መወሰን የለበትም

የትግራይ እናት ልጇን ለጦርነት ሰጠች የሚለው የህወሓት ትርክት የተሳሳተ ነው፤ እናት ልጄ ይሙት ብላ ወደ ጦርነት አትልክም

እኛ ጥያቄያችን አሁን አድጓል፤ ይታፈን የነበረው የባህር በር ጥያቄ ወደ ፊት መጥቷል

መከላከያ ሠራዊት የሚዋጋው ለሥልጣን አይደለም፤ እኛ እዚህ ያለነው አባቶቻችን የሰጡንን ሀገር ለልጆቻችን ለማስተላለፍ ነው

አንቸኩልም፤ ጦርነት አንፈልግም፤ አንቀሰቅስም። በልማታችን ላይ የመጣውን ግን መመከት አለብን፤ የታጠቅነውም ለዚህ ነው

#EBC #ebcdotstream #ENDF #NorthCommand #martyr