ኢትዮጵያ በፈረንጆቹ 2027 የሚካሄደውን የዓለም የአየር ንብረት ጉባዔን (COP32) በአዲስ አበባ እንድታስተናግድ የጉባዔው አባል ሀገራት በመርሕ ደረጃ መስማማታቸውን ሮይተርስ ዘግቧል።
የዘንድሮው የCOP30 ጉባዔ ፕሬዚዳንት አንድሬ ኮሪያ ለሮይተርስ እንደተናገሩት፥ ኢትዮጵያ ዛሬ ምሽቱን የ2027 አስተናጋጅ ሆና ይፋ እንድትደረግ ሀገራት በመርሕ ደረጃ ተስማምተዋል።
ኢትዮጵያ ባሳለፍነው መስከረም ወር ጉባዔውን የማስተናገድ ፍላጎቷን ይፋ ያደረገች ሲሆን፤ የአፍሪካ ሀገራትም ኢትዮጵያ በ2027 የሚካሄደውን የዓለም የአየር ንብረት ጉባዔ (COP32) እንድታስተናግድ በሙሉ ድምጽ መስማማታቸውም ነው የተዘገበው።

የቀጣዩ ዓመት የዓለም የአየር ንብረት ጉባዔ (COP31) አስተናጋጅ ሀገር ማንነት አሁንም ያልተለየ ሲሆን፤ አውስትራሊያ እና ቱርክ ጉባዔውን ለማስተናገድ ጥያቄ አቅርበዋል።
አውስትራሊያ የCOP31 ጉባዔን ለአየር ንብረት ለውጥ ተጋላጭ ከሆኑ ቦታዎች መካከል ቀዳሚ ከሚባሉት የፓሲፊክ ደሴቶች ጋር በመተባበር ለማዘጋጀት ማለሟን አስታውቃለች።
በሰለሞን ከበደ
#ebcdotstream #COP30 #climate #Brazil #Belem #Ethiopia #Africa