Search

የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የ2018 ዓ.ም የታህሳስ እና የጥር ወራት ዋና ዋና የሥራ ክንውኖች

ሰኞ ጥር 25, 2018 233

ባለፉት ሁለት ወራት የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም ለማስጠበቅ፣ ዘላቂ ሰላምን ለማረጋገጥና ሀገራዊ ብልጽግናን ለማፋጠን የተከናወኑ ስትራቴጂያዊ ተግባራት፦ 

ግዙፍ የመሠረተ ልማት እና የኢኮኖሚ ፕሮጀክቶች

• የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ፦ በዓመት እስከ 110 ሚሊዮን መንገደኞችን የማስተናገድ አቅም የሚኖረው ግዙፍ አውሮፕላን ማረፊያ ግንባታ በይፋ ተጀምሯል።

• ታዳሽ ኃይል፦ የአይሻ-2 የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ተመርቆ ወደ ሥራ ገብቷል።

• የፋይናንስ ዘርፍ፦ የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ሪፎርም የሚያፋጥን የ“ፋይናንስ እመርታ” ኮንፈረንስ ተካሂዷል።

• የትራንስፖርት ማሻሻያ፦ በኢትዮ-ጂቡቲ ምድር ባቡር፣ በደረቅ ወደቦችና በመጋዘን ግንባታዎች ላይ የዘመናዊነት ሥራዎች ተጠናክረዋል። 

ቱሪዝም እና ማኅበራዊ ልማት

• ገበታ ለትውልድ፦ የደምቢ ኢኮ ሎጅ እና ሸበሌ ሪዞርት (በ385 ሄክታር ላይ ያረፈ) በይፋ ተመርቀው ለቱሪስቶች ክፍት ሆነዋል።

• የበጎ አድራጎት መንደር፦ ለ150 ዜጎች መኖሪያ የሚሆን የቱሉ አራራ የተቀናጀ ሞዴል መንደር ተመርቋል።

• ትምህርት፦ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ 75ኛ ዓመት የምሥረታ በዓል ላይ የምሁራን ሚናን የተመለከተ ጥናታዊ ጽሑፍ ቀርቧል። 

ብሔራዊ ደህንነት እና ዲፕሎማሲ

• የአየር ኃይል 90ኛ ዓመት፦ የአቪዬሽን ኤክስፖ 2026 እና “የጥቁር አንበሳ” የአየር ላይ ትርዒት በታላቅ ድምቀት ተከብሯል።

• ቀጣናዊ ትብብር፦ የጂቡቲ እና የሶማሊያ መሪዎችን በጅግጅጋ ተቀብሎ በማነጋገር ቀጣናዊ መረጋጋትን የማጠናከር ሥራ ተከናውኗል።

• ዓለም አቀፍ ግንኙነት፦ ከቻይና እና ከዩናይትድ ኪንግደም ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ጋር በሁለትዮሽ ኢንቨስትመንትና በኃይል ማስተላለፊያ ፕሮጀክቶች ላይ ስምምነቶች ተፈርመዋል። 

#PMOEthiopia #AbiyAhmed #Development #EthiopianBroadcastingCorporation #Ethiopia