Search

የ723 ምርጫ ክልሎች ውጤት ፀድቆ ወደ መረጃ ቋት እየገባ ነው - ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ

ረቡዕ ሰኔ 10, 2018 132

 

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሜላት ወርቅ ኃይሉ ለመገናኛ ብዙኃን በሰጡት መግለጫ፥ በአሁኑ ወቅት የሁሉም የምርጫ ክልሎች ውጤቶች ወደ ማዕከል ገብተው የቆጠራ ማጠናቀቂያ ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ገልጸዋል።

በማረጋገጡ ሂደት ላይ ትልቅ ኃላፊነት ተወስዶ ቀን እና ሌሊት ከፍተኛ ርብርብ እየተደረገ መሆኑንም ሰብሳብዋ አብራርተዋል::

 

እንደ ሰብሳቢዋ ማብራሪያ፤ 1 ሺህ 139 የምርጫ ጣቢያዎች መካከል 501 የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እና 638 የክልል ምክር ቤት ውጤቶች ተጠቃልለው ወደ ማዕከል ገብተዋል።

 

ከእነዚህ ውስጥም 723 በቦርዱ ፀድቀው ወደ መረጃ ቋት እየገቡ ይገኛሉ ብለዋል / ሜላትወርቅ።

በተጨማሪም 253 የምርጫ ጣቢያዎች ውጤት የማረጋገጥ እና የኦዲት ሥራ ተከናውኖ ለቦርዱ ለመቅረብ በዝግጅት ላይ እንደሚገኝ ጠቁመዋል።

ይህን የማጣራት ሥራ በላቀ ጥንቃቄ ለማከናወን የውጤት አረጋጋጭ ባለሙያዎች መረጃዎችን ወደ ኦዲት ክፍል በመላክ የመጨረሻ ማረጋገጫ እያደረጉ መሆኑን አክለው ገልጸዋል።

በለሚ ታደሰ