ሀገራዊ ለውጡ እውን መሆን የጀመረበትን 8ኛ ዓመት ምክንያት በማድረግ ለተገኘው ስኬት እውቅና የሚሰጥ በሐረሪ ክልል የሚገኙ የከተማና የገጠር ወረዳዎች ነዋሪዎች የተሳተፉበት የድጋፍ ሰልፍ በኢማም አህመድ ስታዲየም እየተካሄደ ነው።

በስታዲየሙ የተገኙ ተሳታፊዎች የለውጡን ጉዞ የሚደግፉና ለቀጣይ ስኬቶች ያላቸውን ዝግጁነት የሚገልጹ የተለያዩ መልዕክቶችን አስተላልፈዋል።
ከተደመጡት መፈክሮች መካከልም "ሕብረ ብሔራዊ ወንድማማችነት ለዘላቂ ሰላምና ለሁለንተናዊ ብልፅግና!"፣ "እሳቢያችን ዘመን ተሻጋሪ፣ ተግባራችን ትውልድ ቀያሪ!"፣"ሐረርን ከቀደምት ከተማነት ወደ ብልፅግና ተምሳሌትነት እናሸጋግራለን!" የሚሉ ይገኙበታል።

ሰልፈኞቹ መጋቢት 24 በኢትዮጵያ እውነተኛ የዲሞክራሲ ግንባታ የተረጋገጠበትና ሀገሪቱን የማላቅ ጉዞ የተጀመረበት ቀን መሆኑን ገልጸዋል።
እንዲሁም በመስዋዕትነት የተገኘውን ድል በተባበረ ክንድ ለማስቀጠል ያላቸውን ቁርጠኝነት አስተጋብተዋል።
በቴዎድሮስ ታደሰ