Search

የታላቋን ሀገር በጂኦግራፊ እስር ቤት መቆየት የማይፈቅደው የቀይ ባሕር ትውልድ

እሑድ ግንቦት 30, 2018 71

ኢትዮጵያ በዓለም ታሪክ ታይቶ በማይታወቅ መልኩ 130 ሚሊዮን በላይ የሚሆን እጅግ ሰፊ ሕዝብ ይዛ የባሕር በር አልባ ሆና እንድትቀጥል የተፈረደባት ብቸኛ ሀገር ናት።

ይህ ታሪካዊ -ፍትሐዊነት ትውልዱ ላይ ጥልቅ ቁጭት እና የሕልውና ጥያቄ የፈጠረ እና ምላሽ የሚሻ ነው።

ከቅድመ አክሱም ዘመን ጀምሮ እስከ 1985 . ድረስ ኢትዮጵያን እና ቀይ ባሕር ተነጣጥለው አያውቁም።

1985 . እስከ 'መደመር ትውልድ' መነሣት ድረስ ያለው ትውልድ ግን በታሪክ "የሥነ-ልቦና ስብራት" ዘመን ተብሎ የሚታወቅበትን የባዶነት እና የቁጭት ጊዜ አሳልፏል።

በወቅቱ ሥልጣንን የተቆጣጠሩት ኃይሎች ከኢትዮጵያ ታሪካዊ ጠላቶች ጋር ተመሳጥረው ታሪኩን የነጠቁት ትውልድ፣ የባሕር በር ማጣትን እንደማይቀየር ቋሚ ዕጣ ፈንታ በመቁጠር ሲብሰለሰል ኖሯል።

12 በመቶ በላይ የሚሆነው የዓለም የንግድ እንቅስቃሴ የሚተላለፍበትን እና በቅርብ ርቀት ላይ የሚገኘውን ቀይ ባሕርን ዝም ብሎ ማየት ያንገፈገፈው "የመደመር ትውልድ" ዛሬ ተፈጥሯል።

የመደመር ትውልድ 60 በመቶ በላይ የሚሆነውን አምራች እና ወጣት ሕዝብ የሚወክለው የቀይ ባሕር ትውልድ ነው።

ይህ ትውልድ የባሕር በር አልባነትን እንደ ቋሚ ዕጣ ፈንታ ሳይሆን እንደ ታሪካዊ እና ሕጋዊ ስህተት ይመለከተዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (/) በአንድ ወቅት እንደገለጹት፣ 2050 . የሕዝብ ብዛቷ ወደ 150 ሚሊዮን ተብሎ የምትገመተዋ ታላቅ ሀገር መተንፈሻ አልባ ሆና መቀጠል አትችልም።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ደጋግመው እንደገለጹት ይህን ያህል ግዙፍ ሕዝብ ያላትን ሀገር በጂኦግራፊያዊ እስር ቤት ውስጥ አስገብቶ ለቀጣዩ ትውልድ ማውረስ የታሪክ ባለእዳነት ነው።

የቀይ ባሕር ትውልድ ታሪክን የማረም እና የታላቋን ኢትዮጵያን ትክክለኛ የጂኦግራፊ እና የኢኮኖሚ ስፍራ የመመለስ ታሪካዊ አደራ ወድቆበታል።

ይህ ትውልድ የባሕር በር ጥያቄ የፖለቲካ ቅንጦት ሳይሆን፣ 130 ሚሊዮን በላይ ሕዝብ ሕልውና እና የዕድገት መሠረት መሆኑን በሚገባ የተገነዘበ ጠንካራ ሥነ-ልቦና አለው።

የቀይ ባሕር ትውልድ ታሪካዊ ስህተቶችን ለማረም የሚንቀሳቀሰው በጦርነት አዙሪት ሳይሆን፣ በጋራ ተጠቃሚነት፣ በኢኮኖሚያዊ ውህደት እና በብልህ የፓን-አፍሪካኒዝም ዲፕሎማሲ ነው።

ትውልዱ ኢትዮጵያ የምትገነባቸውን ግዙፍ የመሠረተ ልማት ፕሮጀክቶች ከቀይ ባሕር ጂኦ-ፖለቲካዊ ስትራቴጂ ጋር በማስተሳሰር፣ ቀጣናውን የጋራ ብልጽግና ማዕከል ለማድረግ ይተጋል።

በለሚ ታደሰ