Search

"ትግራይ ክልል የጨለማ እና የፍርሃት ድባብ ሆኗል” - ከሞት ያመለጡ የክልሉ ወጣቶች

ሓሙስ ሰኔ 18, 2018 84

ከህወሓት ፅንፈኛው ቡድን የጭቆና ቀንበር እና የሞት ቀጣና ሕይወታቸውን ለማዳን ያመለጡ ወጣቶች ከኢቲቪ ትግርኛ ጋር ባደረጉት ቆይታ፣ በክልሉ ያለውን ዘግናኝ እውነታ ይፋ አውጥተዋል።

ወጣቶቹ እንደሚሉት ፅንፈኛ ቡድኑ የፕሪቶሪያውን የሰላም ስምምነት በግልጽ በመጣስ፣ በክልሉ የራሱንዘግናኝ እና የአራዊት ሕግሲሉ የገለጹትን ሕግ በመደንገግ ሕዝቡ በታላቅ የጨለማ እና የፍርሃት ድባብ ውስጥ እንዲኖር አድርጎታል።

ይህ ሰላም ጠል እና ዘረኛ ቡድን ወጣቶችን ከእናቶቻቸው እቅፍ በሃይል እየነጠቀና እያገተ ወደ ማሰልጠኛና ለንግድ ወደሚሆኑ ቦታዎች እያጎራቸው ይገኛል ብለዋል።

ዛሬ ላይ ከዚህ እኩይ ተግባር ሕይወታቸውን ለማትረፍ የተሰደዱ ወጣቶች፣ መላው ሕዝብ ይህንን የቡድኑን አስነዋሪ ድርጊት በአንድ ድምፅ ሊያወግዘው እና ሊታገለው እንደሚገባ ጥሪያቸውን አቅርበዋል።

በአብርሃ ካሳ