በሪሳ ሹሌ የተባለው የደምቢ ዶሎ ዩኒቨርሲቲ ተማሪ በኤሌክትሪካል እና ኮምፒውተር ኢንጂነሪንግ የትምህርት ክፍል 48 'A+' በማስመዝገብ የወርቅ ሜዳሊያ እና የዋንጫ ተሸላሚ ሆኗል።
ተመራቂው ከ62 የትምህርት ዓይነቶች መካከል 48ቱን 'A+'፣ 12ቱን 'A' እንዲሁም 3ቱን 'A-' በማምጣት በጠቅላላ ነጥብ (CGPA) 3.98 ሊመረቅ ችሏል።
በተጨማሪም በሀገር አቀፉ የሙያ ብቃት ምዘና ፈተና (Exit Exam) ከመቶ 92 ማስመዝገቡ ታውቋል።
በሪሳ ለዚህ ታላቅ ስኬት የበቃበትን ምስጢር ሲናገር፤ ጊዜውን በአግባቡ በመጠቀም እና በሥርዓት ማጥናቱ እንደሆነ መግለጹን ኦቢኤን ዘግቧል።