Search

48 'A+' ያስመዘገበው ባለ ብሩህ አዕምሮ ተማሪ

ቅዳሜ ሰኔ 20, 2018 73

በሪሳ ሹሌ የተባለው የደምቢ ዶሎ ዩኒቨርሲቲ ተማሪ በኤሌክትሪካል እና ኮምፒውተር ኢንጂነሪንግ የትምህርት ክፍል 48 'A+' በማስመዝገብ የወርቅ ሜዳሊያ እና የዋንጫ ተሸላሚ ሆኗል።

ተመራቂው 62 የትምህርት ዓይነቶች መካከል 48ቱን 'A+' 12ቱን 'A' እንዲሁም 3ቱን 'A-' በማምጣት በጠቅላላ ነጥብ (CGPA) 3.98 ሊመረቅ ችሏል።

በተጨማሪም በሀገር አቀፉ የሙያ ብቃት ምዘና ፈተና (Exit Exam) ከመቶ 92 ማስመዝገቡ ታውቋል።

በሪሳ ለዚህ ታላቅ ስኬት የበቃበትን ምስጢር ሲናገር፤ ጊዜውን በአግባቡ በመጠቀም እና በሥርዓት ማጥናቱ እንደሆነ መግለጹን ኦቢኤን ዘግቧል።