የጀጎልን ዓለም አቀፍ ቅርስ ጥንታዊ ይዘትና ሥነ-ሕንጻ ሳይበረዝ ታሪክን ከዘመናዊነት ጋር ያቀናጀው የኮሪደር ልማት ሥራ በ4 ዙሮች ከ22 ኪሎ ሜትር በላይ የውስጥ ለውስጥ መንገዶችን በማልማትና ቀድሞ የቆሻሻ መጣያ የነበሩ ስፍራዎችን ወደ ማራኪ መዝናኛነት በመቀየር እንዲለሙ ተደርገዋል።
ዘመናዊ መሠረተ ልማቶችንና አረንጓዴ ስፍራዎችን ያካተተው ይህ ልማት ለነዋሪዎች ምቾትን ከመፍጠርና ለወጣቶች የሥራ ዕድል ከመክፈት ባለፈ የቱሪስቶችን ቁጥር እና የመቆያ ጊዜ ከፍ ያደረገ ሲሆን "አይቻልም" የሚለውን አስተሳሰብ በተግባር የሰበረ የክልሉ የዕድገት ጉዞ ማሳያ ሆኗል።