Search

በበይነ መረብ የሚሰጠው የ12ኛ ክፍል ሁለተኛ ዙር ሀገር አቀፍ ፈተና ተጀመረ

ዓርብ ሰኔ 26, 2018 58

በበይነ መረብ  እየተሰጠ የሚገኘው 2018 የትምህርት ዘመን 12 ክፍል ማጠቃለያ ፈተና ሁለተኛ ዙር ዛሬ በመላው ሀገራችን መሰጠት ጀምሯል።

ዛሬ የተጀመረው ይህ ሁለተኛ ዙር ፈተና በተፈጥሮ ሳይንስ ዘርፍ ላይ ያተኮረ ሲሆን፣ ተማሪዎች በተመደቡባቸው የፈተና ጣቢያዎች በመገኘት በኮምፒውተር የታገዘውን ፈተና መውሰድ መጀመራቸውን ከትምህርት ሚኒስቴር የተገኘው መረጃ መላክታል።