Search

ከንቲባ አዳነች አቤቤ የአዲስ አበባ ከተማ ፖሊስ ዘመናዊ የፖሊስ የመኖሪያ መንደር ግንባታን አስጀመሩ

ዓርብ ሰኔ 26, 2018 107

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በፖሊስ ተቋም እየሠራቸው ባሉ የሪፎርም ሥራዎች እና ሠራዊቱ በሕዝብ የተጣለበትን አደራ በአግባቡ እንዲወጣ የማድረግ ተግባር፣የሰራዊቱን መንደር እንገነባለንሲል የገባውን ቃል ዛሬ ወደ ተግባር ማሸጋገሩን ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ።

እያደገች እና እየዘመነች ከመጣችው የአፍሪካ እና 3ኛዋ የዓለም የዲፕሎማሲ ማዕከል የሆነችው መዲናችን አዲስ አበባን ለሚያገለግል የፖሊስ ሠራዊት የጀመርነው የመኖሪያ ቤት ግንባታ ባለ 15 ፎቅ  የሆኑ 12 ሕንፃዎች ሲሆኑ፤ የሠራዊቱ አባላትን ማኅበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ጫናዎች በመቀነስ በትጋት እና በአግባቡ ሕዝቡን እንዲያገለግል ለማድረግ ነውብለዋል ከንቲባዋ።

በኮሚሽኑ በከፍተኛ ትጋት የተጀመሩ የሠራዊቱን አባላት በቴክኒክ፣ በእውቀት እና በቴክኖሎጂ ማስታጠቅ የሚያስችሉ ሥራዎች እንዲሁም የሠራዊቱን ሕይወት ለማሻሻል የተጀመሩ የሪፎርም ሥራዎች ውጤታማ እንዲሆኑ ድጋፋችንን እጠናክረን እንቀጥላለን ሲሉም አረጋግጠዋል።