Search

ከሃይል ስርቆት ጋር በተያያዘ አንድ ሺህ ቆጣሪዎች ተይዘዋል፦ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት

ዓርብ ነሐሴ 09, 2017 1069

ተቋሙ  ከሃይል ሽያጭ እና  ከተለያዩ ገቢዎች  63 ቢሊዮን በላይ ብር  ገቢ መስብሰቡንም ዋና ሥራ አስፈፃሚው ኢንጂነር ጌቱ  ገረመው ተናግረዋል።

ዋናሥራ አስፈጻሚው ለመገናኛ ብዙሃን በሰጡት መግለጫ ከ8 ሺህ 350 ባላይ ከተሞች እና መንደሮች የአግልግሎቱ ተጠቃሚበማደርግ ሀገራዊ የኤሌክትሪክ ተደራሽንት 54 በመቶ ደርሷል ብለዋል።

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገለግሎት ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር ጌቱ  ገረመው

አገልግሎቱ አሁን ላይ 5.2 ሚሊዮን በላይ ደንበኞች እንዳሉት የገለጹት ዋና ሥራ አስፈጻሚው በ2017 በጀት ዓመት በዋናው የሃይል ቋት እና ከዋናው የሃይል ቋት ውጭ 155 ቀበሌዎች የኤሌክትሪክ አገልግሎት እንዲያገኙ ማደረግ መቻሉ ገልጸዋል።

የሃይል ስርቆት ጋር በተያያዘ አንድ ሺህ የሚሆኑ ቆጣሪዎች መያዛቸውንበመግለጽ የሃይል መቆራረጥችግርን የጥገናእና የማስፋፊያ ሥራ መሰራቱን ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት መግለጫ 

የአገልግሎት አሰጣጥ ላይ ያሉ ችግሮችን ለመፍታት እየተሰራ ባለው ሥራ  94.8 በመቶ ደንበኞች የአገልግሎት ክፍያቸውን በዲጂታል መንገድ እንዲከፍሉ ማድረግ ተችሏል።

በ2018  አገልግሎቱ ከሃይል ሽያጭ 74 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ ለማግኘት እና አጠቃላይ ገቢውን 101 ቢሊዮን ለማድረስ ማቀዱን ተናግረዋል

አቤል ሙሉጌታ