ውበታችን በአንድነታችን፣ ጥንካሬያችን ደግሞ በህብረታችን ውስጥ ጉልህ ሆኖ ይንጸባረቃል። ከልዩነት ይልቅ አንድነትን፣ ከመለያየት ይልቅ መሰባሰብን መርጠን እጅ ለእጅ ስንያያዝ ምድራችንን የለመለመች ገነት ማድረግ እንችላለን።
ኑ! የተሰጠንን የተፈጥሮ ጸጋ አሟጠን በመጠቀም፣ በፍቅር እና በትጋት ሀገራችንን ወደ ተሻለ ከፍታ እናሻግራት። በመተባበር መሬታችንን እናልብስ፤ ኢትዮጵያችንን በጋራ እናለምልም!