Search

በልዩ ጥበቃ የታጀበው የኃያላኑ ሀገራት ፕሬዚዳንቶች ውይይት

ዓርብ ነሐሴ 09, 2017 154

የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ እና የሩሲያው ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን በአንከሬጅ አላስካ አየር ማረፊያ ተገናኝተው እጅ ለእጅ ተጨባብጠዋል።

በአየር ማረፊያው በርካታ የጦር ጀቶች የታዩ ሲሆን፣ ጥበቃውም ከበድ ያለ እንደሆነ ዓለም አቀፍ መገናኛ ብዙሃን እየዘገቡ ነው።

በአላስካ አየር ማረፊያ በዘተጋጀላቸው ቀይ ምንጣፍ ላይ ሆነው እጅ ለእጅ ከተጨባበጡና የፎቶ ግራፍ መነሳት ስነ-ስርዓት አከናውነዋል።

ከዚህም በኋላ ዓለም በጉጉት ወደሚጠብቀው ውይይት ያመሩ ሲሆን፤ በከባድ መሳሪያ የታገዘ ጥበቃ እየተደረገላቸው መሆኑም ተዘግቧል።

የልዑካን ቡድናቸው ይዘው ወደስብሰባው ስፍራ የገቡት ፕሬዚዳንቶቹ በዩክሬን ጉዳይ ላይ እንዲሁም በሁለቱ ሀገራት ግንኙነት ላይ ይመክራሉ ተብሎ ይጠበቃል።

#EBC #ebcdotstream #russia #usa