በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ከ1988 እስከ 2000 ዓ.ም ፕሬዚዳንት በመሆን ያገለገሉት አቶ ከማል በድሪ ባደረባቸው ሕመም በሕክምና ሲረዱ ቆይተው ዛሬ ሐምሌ 08 ቀን 2018 ዓ.ም ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል።
ሥርዓተ ቀብራቸው የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት አቶ ቴዎድሮስ ምህረትን ጨምሮ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃፊዎች በተገኙበት ዛሬ ከቀኑ 9 ሰዓት ላይ ተፈጽሟል።
የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በቀድሞው ፕሬዚዳንት አቶ ከማል በድሪ ኅልፈት የተሰማውን ጥልቅ ኀዘን ገልፆ፤ ለቤተሰባቸው እና ለወዳጅ ዘመዶቻቸው መጽናናትን ተመኝቷል።
አስተያየትዎን እዚህ ያስፍሩ: