Search

የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የቀድሞ ፕሬዚዳንት አቶ ከማል በድሪ ሥርዓተ ቀብር ተፈፀመ

ረቡዕ ሐምሌ 08, 2018 98

በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት 1988 እስከ 2000 . ፕሬዚዳንት በመሆን ያገለገሉት አቶ ከማል በድሪ ባደረባቸው ሕመም በሕክምና ሲረዱ ቆይተው ዛሬ ሐምሌ 08 ቀን 2018 . ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል።

ሥርዓተ ቀብራቸው የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት አቶ ቴዎድሮስ ምህረትን ጨምሮ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃፊዎች በተገኙበት ዛሬ ከቀኑ 9 ሰዓት ላይ ተፈጽሟል።

የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በቀድሞው ፕሬዚዳንት አቶ ከማል በድሪ ኅልፈት የተሰማውን ጥልቅ ኀዘን ገልፆ፤ ለቤተሰባቸው እና ለወዳጅ ዘመዶቻቸው መጽናናትን ተመኝቷል።

አስተያየትዎን እዚህ ያስፍሩ: