በትግራይ ክልል እየተባባሰ የመጣውን ቀውስ ለመቃወም እንዲሁም ለፌደራል መንግሥትና ለዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ መልዕክት ለማስተላለፍ “አፈሳ ይቁም፣ ሰላም ይስፈን” በሚል መሪ ቃል ነገ ሐምሌ 11 ቀን 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 12:00 ሰዓት ጀምሮ በመስቀል አደባባይ ሰላማዊ ሰልፍ ይደረጋል።
በመሆኑም ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስዱ መንገዶች ከንጋቱ 11:00 ሰዓት ጀምሮ ፕሮግራሙ እስከሚጠናቀቅ፣
ከመገናኛ በ22 አደባባይ ወደ መስቀል አደባባይ፣ ዑራኤል አደባባይ ላይ፣
በቦሌ መንገድ ወደ መስቀል አደባባይ፣ ኦሎምፒያ አደባባይ ላይ፣
ከጎተራ ወደ መስቀል አደባባይ፣ ለከባድ ተሽከርካሪ አጎና ሲኒማ መስቀለኛ ላይ፣ ለቀላል ተሽከርካሪ ጥላሁን አደባባይ ላይ፣
ከሜክሲኮ አደባባይ ወደ መስቀል አደባባይ፣ ለገሀር መብራት ላይ፣
ከለገሀር ቴሌ ማቋረጫ ወደ ስታዲየም፣ ለገሀር ቴሌ ማቋረጫ ላይ፣
ከአራት ኪሎ ወደ መስቀል አደባባይ፣ ብሔራዊ ቤተ-መንግሥት ላይ፣
ከካሳንቺስ በመቅረዝ ሆስፒታል ወደ መስቀል አደባባይ፣ መቅረዝ ሆስፒታል አጠገብ፣
ከአምባሳደር ቴአትር ወደ መስቀል አደባባይ፣ ሐራምቤ መብራት ላይ ዝግ እንደሚሆኑ የአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ አስታውቋል።
በተጨማሪም ከዛሬ ሐምሌ 10 ቀን 2018 ዓ.ም ከምሽቱ 12፡00 ሰዓት ጀምሮ በመስቀል አደባባይና በዙሪያው ባሉ መንገዶች ተሽከርካሪ ለአጭርም ሆነ ለረጅም ጊዜ ማቆም የተከለከለ መሆኑን ዋና ጠቅላይ መምሪያው ገልጿል።
አስተያየትዎን እዚህ ያስፍሩ: