የመሶብ አገልግሎት ዘላቂና ተደራሽ ለማድረግ ለቀጣይ ሦስት ዓመታት የመሶብ አገልግሎት የሚመራበት ስትራቴጅክ ዕቅድ በፌዴራል መሶብ አገልግሎት ተዘጋጅቷል።
የፌደራል፣ የከተማ አስተዳደሮች እና የክልል መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት የሥራ ኃላፊዎች በስትራቴጂክ ዕቅዱ ላይ ውይይት እያደረጉ ይገኛሉ።
በ2017 ዓ.ም ተግባራዊ የተደረገውና መንግሥታዊ አገልግሎቶችን ፈጣን፣ ቀልጣፋ እና ከብልሹ አሠራር የፀዳ ለማድረግ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት፣ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ተጀምሮ፣ አሁን ላይ በሁሉም ክልሎች 100 የመሶብ አገልግሎት መስጫ ማዕከላት ወደ ሥራ መግባታቸው ተገልጿል።
በተጨማሪም በአዲስ አበባ ከተማ ሦሶት ተንቀሳቃሽ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ሰጪዎች እና ዜጎች ባሉበት ሆነው አገልግሎት የሚያገኙበት የተቀናጀ የዲጂታል አገልግሎት መተግበሪያ በዚህ ዓመት ወደ ሥራ መግባቱ ተመላክቷል።
በፌዴራል መሶብ አገልግሎት የተዘጋጀው ስትራቴጂው፣ ከ2019 እስከ 2021 ዓ.ም የሚተገበር ሲሆን፣ መሶብ አገልግሎት ተቋማዊ አሠራሩን ለማዘመን፣ የአገልግሎት ጥራትን ለማሻሻልና ተደራሽነቱን ለማስፋት የሚያስችሉ ትልሞችን ይዟል።
በስትራቴጅው መሠረት በመጪዎቹ ሦስት ዓመታት በሁሉም ወረዳዎች መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ተደራሽ እንደሚደረግና ተንቀሳቃሽ እና ራስ አገዝ የመሶብ አገልግሎትን ለማስፋት እንደሚሠራ ተገልጿል።
በባዬ ሙላት
አስተያየትዎን እዚህ ያስፍሩ: