Search

በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ5.7 ቢሊዮን ዶላር በላይ ከማዕድን ወጪ ንግድ ተገኝቷል - የማዕድን ሚኒስትር ኢንጂነር ሀብታሙ ተገኘ

ሓሙስ ሐምሌ 30, 2018 52

የማዕድን ሚኒስቴር 2018 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈፃፀም እና 2019 በጀት ዓመት ዕቅድ ግምገማ ውይይት እያካሄደ ነው።

ማዕድን የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ምሶሶ በመሆን ምጣኔ ሀብቱ ላይ ከፍተኛ ለውጥ እያመጣ መሆኑን ሚኒስትሩ ኢንጂነር ሀብታሙ ተገኘ ተናግረዋል።

በበጀት ዓመቱ በማዕድን ዘርፍ ስኬታማ ሥራዎች መሠራታቸውን እና አመርቂ አፈጻጸም መመዝገቡን ሚኒስትሩ ጠቅሰዋል።

በኩባንያዎች እና ከባህላዊ ወርቅ አምራቾች 44 ቶን በማምረት 5.65 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ተገኝተዋል። ከዚህ በተጨማሪም 271 በላይ ሰዎች ከዘርፉ ቋሚ የሥራ ዕድል ተፈጥሯል።

በዘርፉ የኢንቨስትመንት ፈቃድ በመስጠት እና ተኪ ምርቶችን በማምረት ረገድም ተጨባጭ ውጤት መመዝገቡን ሚኒስትሩ ተናግረዋል።

በአጠቃላይ በበጀት ዓመቱ ከወጪ ንግድ ማዕድናት 5.7 ቢሊዮን ዶላር መገኘቱን ኢንጂነር ሀብታሙ ተገኘ አስታውቀዋል።

ሚኒስትሩ የማዕድን ዘርፍ ከአምስቱ የሀገራችን የኢኮኖሚ ምሰሶዎች አንዱ መሆኑን ገልጸው፣ ባለፉት ዓመታት የዘርፉ ዕድገት በፍጥነት እየጨመረ መምጣቱን አመላክተዋል።

በቀጣይም 6.7 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ለማግኘት ታቅዶ እየተሠራ እንደሚገኝ ጠቅሰዋል።

በአባዲ ወይናይ

 

አስተያየትዎን እዚህ ያስፍሩ: