Search

የቅዱስ ገብርኤል ዓመታዊ የንግሥ በዓል በቁልቢ እና በሐዋሳ እየተከበረ ነው

እሑድ ሐምሌ 19, 2018 56

በየዓመቱ ሐምሌ 19 ቀን የሚከበረው የቅዱስ ገብርኤል ዓመታዊ የንግሥ በዓል በቁልቢ ደብረ ኃይል ቅዱስ ገብርኤል ገዳም እና በሐዋሳ ከተማ በሃይማኖታዊ ሥርዓት በመከበር ላይ ይገኛል።

በዓሉ የሃይማኖት አባቶች፣ ምዕመናን እንዲሁም የሀገር ውስጥና የውጭ ሀገራት እንግዶች በተገኙበት በመንፈሳዊ ሥርዓት እየተከበረ ነው።

በቁልቢ ቅዱስ ገብርኤል ገዳም እየተካሄደ ባለው የንግሥ በዓል ሥርዓት ላይ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ጠቅላይ ቤተ ክህነት ሥራ አስኪያጅ ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ፣ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ እና ሌሎች ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ተገኝተዋል።

 

በሐዋሳ ከተማ እየተከበረ በሚገኘው የንግሥ በዓል ላይ ደግሞ የሲዳማ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ዮሴፍ ተገኝተው በዓሉን ከምዕመናን ጋር በጋራ እያከበሩ ይገኛሉ።

አስተያየትዎን እዚህ ያስፍሩ: