Search

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች የአመራር ምርጫ በመላ ሀገሪቱ በሰላም ተጠናቋል - የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ም/ቤት የ2017 ምርጫ አስፈፃሚ ቦርድ ጽ/ቤት

እሑድ ነሐሴ 11, 2017 114

መላው የኢትዮጵያ ሙስሊም ማህበረሰብ ዑለማዎች፣ ምሁራኖች፤ ወጣቶች፣ ሴቶችና የሥራ ማህበረሰብ የ2017 የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች የአመራር ምርጫ በመላ ሀገሪቱ የመጀመሪያ ደረጃ የመስጂድ ምርጫ ሲካሄድ ቆይቶ በስላም መጠናቀቁን የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ም/ቤት የ2017 ምርጫ አስፈፃሚ ቦርድ ጽ/ቤት ለኢቢሲ በላከው መግለጫ  አስታውቋል።

ሁሉም ክልሎች ምርጫውን ከነሐሴ 9/ 2017 በዑለማዎች ጀምሮ ዛሬ ነሐሴ 11/ 2017 በአራቱ ዘርፎች ማለትም በምሁራን፣ ወጣቶች፣ ሴቶችና የሥራ ማህበራት እስከ ቀነ- 12 ሰዓት ድረስ በመምረጥ መጠናቀቁም ተገልጿል።

ምርጫውን በማስተባበር፣ በመምራት እንዲሁም አጠቃላይ ይዘቱ መስመሩን ይዞ እንዲሄድ ላደረጋችሁት ተሳትፎ፣ ከመንግሥት ለተደረገው የፀጥታ ድጋፍ ምስጋናችን የላቀ ነው ብሏል የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ም/ቤት የ2017 ምርጫ አስፈፃሚ ቦርድ ጽ/ቤት።  

የቀሩትን ከወረዳ እስከ ፌደራል የምክር ቤት ምስረታዎች በጉልህ፣ በሙሉ ሞራል፣ ተሳትፎ እና ተነሳሽነት ይካሄድ ዘንድም ም/ቤቱ መልዕክት አስተላልፏል።