Search

በናይጄሪያ በደረሰ የጀልባ መስመጥ አደጋ የ10 ሰዎች ሕይወት አለፈ

Aug 18, 2025

በናይጄሪያ ሶኮቶ ግዛት፣ 50 በላይ ሰዎችን አሳፍራ ስትጓዝ የነበረች ጀልባ ባጋጠማት የመስመጥ አደጋ 10 ሰዎች ሕይወት ማልፉ ተዘገበ

በደረሰው የጀልባ መስመጥ አደጋ 40 በላይ ሰዎችን እስካሁን ማግኘት እንዳልተቻለም ነው የተገለፀው።

የነፍስ አድን ሠራተኞች የጠፉ ሰዎችን ፍለጋ ላይ መሆናቸውን የሀገሪቱ የድንገተኛ አደጋ ተቋም አስታውቋል።

በተመሳሳይ ከሁለት ቀናት በፊት በማዕከላዊ ኒጀር ግዛት በሌላ የጀልባ አደጋ ቢያንስ 13 ሰዎች መሞታቸው ይታወሳል

በናይጄሪያ ከጥገና ጉድለት እና በዝናብ ወቅት በሚከሰት ጎርፍ ምክንያት የጀልባ አደጋዎች በተደጋጋሚ ይከሰታሉ ሲል ሲጂቲኤን ዘግቧል።

በሴራን ታደሰ