Search

የአርቲስት ደበበ እሸቱ ሥርዓተ ቀብር ነገ ይፈጸማል

ሰኞ ነሐሴ 12, 2017 171

የአርቲስት ደበበ እሸቱ ሥርዓተ ቀብር ነገ ነሀሴ 13 ከቀኑ 8 ሰዓት ላይ 4 ኪሎ  መንበረ  ጸባኦት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ይፈፀማል።

በነገው ዕለትም ከረፋዱ 5 ሰዓት ጀምሮ በብራዊ ቴአትር ቤተሰቦቹ፤ ወዳጅ ዘመዶቹ እና የሙያ አጋሮቹ በተገኙበት የአስክሬን ሽኝት  የሚደረግለት ይሆናል።

የአርቲስት ደበበ እሸቱ ባደረባቸው ህመም ምክንያት በህክምና ሲረዱ ቆይተው 83 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም ድካም አርፈዋል።

የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ዴዔታ ነብዩ ባዬ እና የሙያ አጋሮቹ በመግለጫው ወቅት በአርቲስት ደበበ እሸቱን ሕልፈት የተሰማቸዉን ሀዘን ገልጸዋል።
በቢታኒያ ሲሳይ