Search

የኢትዮጵያ የመጀመሪያው የዐይን ሐኪም ዶክተር ጳውሎስ ቀነዓ አረፉ

ሰኞ ነሐሴ 04, 2018 123

የኢትዮጵያ የመጀመሪያው የዐይን ሐኪም እና የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የዓይን ሕክምና ትምህርት ክፍል መሥራች ዶክተር ጳውሎስ ቀነዓ 97 ዓመታቸው አርፈዋል።

በዳግማዊ ምኒልክ ሆስፒታል ለረጅም ዓመታት ያገለገሉት ዶክተር ጳውሎስ፣ ከማከም አልፈው በሀገራችን የነበረውን የዐይን ሐኪሞች እጥረት ለመቅረፍ 1972 . የዐይን ሕክምና የድህረ ምረቃ ትምህርት ክፍልን በማስጀመር በርካታ ባለሙያዎችን አፍርተዋል።

ጤና ሚኒስቴር ዛሬ ባጋራው መግለጫ፣ በእኚህ አንጋፋ እና ለብዙዎች አርዓያ በሚሆኑ የጤና ባለሙያ ሕልፈተ ሕይወት የተሰማውን ጥልቅ ኀዘን በመግለጽ ለቤተሰቦቻቸው እና ወዳጅ ዘመዶቻቸው መፅናናትን ተመኝቷል።

አስተያየትዎን እዚህ ያስፍሩ: