ፕሬዚዳንት ታየ አጽቀ ሥላሴ የታይላንድ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሲሀሳክ ፉዋንግኬትኬዎን በብሔራዊ ቤተ መንግሥት ተቀብለው አነጋገሩ።
በውይይታቸው ወቅት በኢትዮጵያ እና በታይላንድ መካከል ስላለው የረጅም ጊዜ ግንኙነት ሰፊ ምክክር ማድረጋቸውን የፕሬዚዳንት ጽ/ቤት አስታውቋል።
የሁለቱን ሀገራት የሁለትዮሽ ግንኙነት እና የትብብር መስኮችን ይበልጥ ማጠናከር እና ማሳደግ በሚቻልባቸው ዕድሎች ዙሪያም ሐሳብ መለዋወጣቸው ተገልጿል።
አስተያየትዎን እዚህ ያስፍሩ: