በ2ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ስታምፎርድ ብሪጅ ላይ ብራይተንን ያስተናገደው ቼልሲ 4 ለ 3 በሆነ ውጤት አሸንፏል።
ሮሚዮ ላቪያ ለቼልሲ የመጀመሪያውን ግብ ባስቆጠረበት ጨዋታ፣ ፔድሮ ኔቶ እና ጆዋዎ ፔድሮ ተጨማሪ ግብ አስቆጥረው ቼልሲ 3 ለ 0 እንዲመራ አስችለው ነበር።
ሆኖም ማሊክ ጁኒየር ለብራይተን አስቆጥሮ የመጀመሪያው አጋማሽ በቼልሲ 3 ለ 1 መሪነት ተጠናቅቋል።
በሁለተኛው አጋማሽ ጆዋዎ ፔድሮ በራሱ መረብ ላይ ያስቆጠራት ግብ ውጤቱን ወደ 3 ለ 2 ብታጠብም፣ ኮል ፓልመር ተጨማሪ ግብ አስቆጥሮ ቼልሲን 4 ለ 2 መሪ አድርጓል። በጭማሪ ሰዓት ፓስካል ግሮስ ያስቆጠራት ግብ ብራይተንን ከሽንፈት አልታደገችም።
ጨዋታው 4 ለ 3 በሆነ ውጤት መጠናቀቁን ተከትሎ ቼልሲ በሁለት ተከታታይ ደሎቹ ነጥቡን ስድስት ሲያደርስ፣ በሁለቱ ጨዋታዎች በተጋጣሚዎቹ መረብ ላይ ያስቆጠራቸው ግቦች 7 ሆነዋል።
ቼልሲ በ3ኛው ሳምንት የሊጉ መርሐ-ግብር በቀጣይ ሳምንት እሁድ ሻምፒዮኑን አርሰናል በኢሚሬትስ ይገጥማል።
አስተያየትዎን እዚህ ያስፍሩ: