በ5ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ማንቸስተር ሲቲ ሰንደርላንድን 5 ለ 3 በማሸነፍ የደረጃ ሰንጠረዡን በ3 ነጥብ ልዩነት መምራት ጀምሯል።
በኢቲሃድ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ የማንቸስተር ሲቲን የማሸነፊያ ግቦች ኤንዞ ፈርናንዴዝ፣ ራያን ቸርኪ፣ አንቶይን ሴሜኒዮ(ሁለት) እንዲሁም ኤርሊንግ ሃላንድ አስቆጥረዋል።
ሰንደርላንድን ከሽንፈት ያልታደጉትን ሦስቱንም ግቦች ከመረብ በማሳረፍ ሀትሪክ የሰራው ደግሞ ብሪያን ሮቤይ ነው።
ባለ ድሉ ማንቸስተር ሲቲ አርሰናል ትላንት መሸነፉን ተከትሎ 15 ነጥብ በመሰብሰብ የደረጃ ሰንጠረዡን በ3 ነጥብ ልዩነት መምራት ሲጀምር፣ ሰንደርላንድ በ4 ነጥብ 14ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል።
ወደ ቫይታሊቲ ስታዲየም አቅንቶ ቦርንመዝን የገጠመው ሊቨርፑል በአልክሳንደር ኢሳክ ብቸኛ ግብ 1 ለ 0 በመርታት በውድድር ዓመቱ 2ኛ ድሉን አስመዝግቧል። በደረጃ ሰንጠረዡም 6ኛ ላይ ተቀምጧል።
ሊድስ ዩናይትድ ከ ክሪስታል ፓላስ ያደረጉት ሌላኛው ጨዋታ ያለ ግብ 0 ለ 0 ተጠናቅቋል።
አስተያየትዎን እዚህ ያስፍሩ: