Search

ከ7 ዓመታት የስደት ኑሮ በኋላ በሀገሩ የተረጋጋ ሕይወት መምራት የጀመረው ወጣት

ረቡዕ ነሐሴ 21, 2017 119

ወጣት እሸቱ ሶራቶ የወላይታ ሶዶ ከተማ ነዋሪ ሲሆን፤ 7 ዓመታት አስቸጋሪ የስደት ኑሮ በኋላ በሀገሩ የተረጋጋና አስደሳች ሕይወት እየመራ መሆኑን ይናገራል።

ከዓመታት በፊት በአቻ ግፊት የተሻለ ሕይወት ፍለጋ መዳረሻውን አውስትራሊያ አድርጎ ከእናት ሀገሩ በኬኒያ በኩል መሰደዱን ያስታውሳል።

ሆኖም ጉዞው እንዳሰበው አልሆነም፤ ከዚህም የተነሳ ለ7 ድፍን ዓመታት ካሰበበት ሳይደርስ በተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት ሲንከራተት ቆይቷል።

ረሀብ፣ ጥም፣ በጀልባ ላይ ለበርካታ ቀናት መቆየት እና በሕገ-ወጥ ደላላዎች የሚፈፀሙ ክህደቶች የስደት ሕይወቱን አስቸጋሪ እንዳደረጉበት ይገልፃል።

ወጣት እሸቱ ስደት በቃኝ ብሎ ከዛንዚባር ወደ ሀገሩ ከተመለሰበት ጊዜ አንስቶ ለወጣቶች የስደትን አስከፊ ገፅታተሞክሮው እያጋራ ይገኛል።

ከዚህ ባሻገር ከስደት መልስ በሀገሩ በመሥራት በሕይወቱ ላይ ያመጣው ለውጥም በሀገር ሰርቶ መለወጥ እንደሚቻል ጥሩ ማሳያ ሆኗል።

2010 . ከጓደኞቹ ጋር በማህበር ተደራጅተው የከፈቱት የወጣቶች መዝናኛ ማዕከል 5 ቋሚ እና 7 ጊዜያዊ የሥራድል ፈጥሯል።

ከዚህ ጎን ለጎን የከብት እርባታ በመጀመር 14 የወተት ላሞች ባለቤት መሆን የቻሉት ወጣቶቹ፤ ከላሞቹ የሚገኘውን ወተት ለደንበኞቻቸው ጭምር በማከፋፈል ላይ ይገኛሉ።

ወጣት እሸቱ በግሉም መሀል ሶዶ ከተማ ላይ የጀበና ቡና መሸጫ የከፈተ ሲሆን፤ የኢንቨስትመንት ፈቃድ በማውጣት 8 ሺህ ካሬ ሜትር ቦታ ላይ የከብት እርባታ ሥራ ለመጀመር ዝግጅቱን አጠናቅቋል። በዚህም 100 ወጣቶች የሥራ ዕድል ለመፍጠር አቅዷል።

ወጣቶች በርትተውሰሩ ኢትዮጵያ ለብዙዎች የሚተርፍ ሀብት አላት ሲል ወጣት እሸቱ ምክሩን ለግሷል።

በተመስገን ተስፋዬ

#EBCdotstream #Youths #Entrepreneurship #Migration